የኢትዮጵያን እናድን አባላትና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተወካዮች በውጭ ምንዛሪ ዙሪያ ተወያዩ

*** "ኢትዮጵያ የልጆቿን ድጋፍ ከምንም በላይ በምትፈልግበት ወቅት ወደ ግብር የለወጣችሁ የኢትዮጵያን አናድን አባላትን በራሴና በሚሲዮኑ ስም አመሰግናለሁ" አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድር

 Ayelew Hundessa (C).

Ayelew Hundessa (C). Source: SBS Amharic

በአውስትራሊያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ  "ኢትዮጵያን እናድን" ፋይናንስ አባላት ዛሬ ሴፕቴምበር 25 ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ። 

ውይይቱን የመሩት የኢትዮጵያን እናድን አስተባባሪ አቶ አያሌው ሁንዳሳ የዕለቱን አጀንዳ አስተዋውቀዋል። 

ውይይቱን በንግግር የከፈቱት በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድር ናቸው።

አምባሳደሩ በንግግራቸው "ኢትዮጵያ የልጆቿን ድጋፍ ከምንም በላይ በምትፈልግበት ወቅት ወደ ግብር የለወጣችሁ የ Save Ethiopia አባላትን በራሴና በሚሲዮኑ ስም አመሰግናለሁ። Save Ethiopia ወቅታዊና ትክክለኛ platform ነው" ብለዋል።
Ambassador Dr Muktar Kedir.
Ambassador Dr Muktar Kedir. Source: SBS Amharic
ከአምባሳደሩ ንግግር በመቀጠል አቶ ለማ ዋቀዮ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳያስፖራ ተሳትፎና ቢዝነስ ሥራ አስፈፃሚ የውጭ ምንዛሪ ምንጮችንና የኢትዮጵያን እናድንን ጥረት አስመልክተው ተናግረዋል። 

የኢትዮጵያ ምንዛሬ ምንጮች ውስን መሆናቸውን ጠቁመው፤ በዋነኛነት የውጭ ብድር፣ እርዳታ፣ የውጭ አቅርቦትና ሃዋላ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ከእነዚህም ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዙት የውጭ ብድርና እርዳታ መሆናቸውን ጠቁመው፤ የውጭ አቅርቦት ገቢ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት የሚጠይቀውን ያህል  አለመሆኑን ገልጠዋል።
Lemma Waqeyo.
Lemma Waqeyo. Source: SBS Amharic
አያይዘውም "የኢትዮጵያን እናድን ተነሳሽነት ትክክለኛም ወቅታዊም ነው። የውጭ ምንዛሬ ክፍተቱን ለመድፈንም ያስችላል። ካላችሁበት አገር ሆናችሁ ያላችሁን ገንዘብ እዚህ [ኢትዮጵያ] ማስቀመጥ ትችላላችሁ። ልዩነቱ አድርሻ መለወጥ ብቻ ነው። ይህን ማድረግ አገርን ማገዝ ነው። የጥቁር ገበያው ከምጣኔ ሃብት ጉዳት አልፎ የሰው ሕይወትን ጭምር እያጠፋ ነው" ብለዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሃዋላ ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሐንስ ሊቁ በበኩላቸው "የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውጭ ካሉ 60 በላይ ባንኮች ጋር ገንዘብ ከአገር ውስጥ ወደ ውጭ፤ ከውጭ ወደ አገር ውስጥ በማሸጋገር ላይ ይገኛል። ውጭ ያለው ገንዘብ ወደ አገር ውስጥ ገብቶ ተቀመጠ ማለት ከ80 ፐርሰንት ለመንግሥት (የመንገድና ቴሌኮም አገልግሎቶች፣ የውጭ አገር መምህራን ደመወዝ ለመሳሰሉት) 20 ፐርሰንት ለግል ፕሮጄክቶች ይውላል" ሲሉ ተናግረዋል።
Yohannes Liku.
Yohannes Liku. Source: SBS Amharic
በውጭ አገር ነዋሪ ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቁጠባና የቤት ግዢና ግንባታን ጨምሮ የተለያዩ የባንክ ሂሳቦችን የመክፈትና የወለድ ጥቅሞችንንም የሚያስገኙ ግልጋሎቶችን እንደሚሰጥ አብራርተዋል። 

በአጀንዳው መሠረትም ዶ/ር ከፋለ መኮንንና አቶ ግርማ ፈይሳ የኢትዮጵያን እናድን ተነሳሽነት ዓላማ፣ እስካሁን የተደረጉ እንቅስቃሴዎች፣ ታሪካዊና ወቅታዊ የውጭ ምንዛሪ እጥረትና እርዳታን አስመልክተው ለታዳሚዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል።             


Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service