የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፤ አውስትራሊያ በቅርብ ቀናት ውስጥ ሙሉ ክትባት የተከተቡ ሰዎች ቁጥር 80 ፐርሰንት ሊያልፍ ነው

*** ቪክቶሪያ ውስጥ 1,247 ነዋሪዎች በቫይረስ ተጠቅተዋል፤ ዘጠኝ ለሕልፈተ ሕይወት ተዳርገዋል።

COVID-19 update

House in the Sydney suburb of Blacktown lit up for Diwali. Source: SBS

ፋይዘር ዕድሜያቸው ከ5 እስከ 11 ላሉ ልጆች ክትባት መስጠት እንዲችል የፈዋሽ ቁሶች አስተዳደር ይሁንታን ለማግኘት ማመልከቻ ማስገባቱን የፌዴራል ጤና ሚኒስትር ግሬግ ሃንት አስታወቁ። 

በቀጣይነትም ከአውስትራሊያ የክትባት ቴክኒካዊ አማካሪ ቡድን ዕድሜያቸው ይሁንታ እንደተገኘም ዕድሜያቸው ከ5 እስከ 11 ላሉ ልጆች ክትባት መስጠት ይጀመራል። 

አቶ ሃንት በመጪዎቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ ሙሉ ክትባት የተከተቡ አውስትራሊያውያን ቁጥር 80 ፐርሰንት እንደሚያልፍ ተናግረዋል። 

በሌላ በኩል ኩዊንስላንድ በምትገኘው ጉንዲዊንዲ ከተማ ኮሮናቫይረስ በመከሰቱ የምርመራ ጣቢያዎች ተቋቁመዋል። ይሁንና ከተማይቱ ላይ ገደቦች አልተጣሉም። 

ከዛሬ ጀምሮ የሚካሔደውን የዲዋሊ ክብረ በዓል ተከትሎ የኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕል ጤና ኮሚሽን አገልግሎት የተወሰኑ ምክረ ሃሳቦችን ሰጥቷል። 
COVID-19 update
Source: NSW Health
ኮቪድ-19 ስታቲስቲክስ

  • ቪክቶሪያ ውስጥ 1,247 ነዋሪዎች በቫይረስ ተጠቅተዋል፤ ዘጠኝ ለሕልፈተ ሕይወት ተዳርገዋል።
  • ኒው ሳውዝ ዌይልስ ውስጥ 308 በቫይረስ ተጠቅተዋል፤ ዘጠኝ ለሕልፈተ ሕይወት ተዳርገዋል።
  • ኩዊንስላንድ ውስጥ ሶስት ሰዎች በቫይረስ ተጠቁ።
  • የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ውስጥ 13 ሰዎች በቫይረስ ተጠቅተዋል።
የክትባት አሰጣጥ

የማጠናከሪያ ሶስተኛ ዙር ክትባት ኖርዘር ቴሪቶሪ ውስጥ ከሰኞ ኖቬምበር 8 ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል፤ ሆኖም ግዴታ አይሆንም።


Share

Published

By SBS/ALC Content
Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፤ አውስትራሊያ በቅርብ ቀናት ውስጥ ሙሉ ክትባት የተከተቡ ሰዎች ቁጥር 80 ፐርሰንት ሊያልፍ ነው | SBS Amharic