መሪዎችና የሃይማኖት አባቶች የኢድ አልፈጥር መልካም ምኞት መልዕክቶችን አስተላለፉ

*** “የኢትዮጵያውያን ዕድል በእኛው እንጂ በሌላ በማንም እጅ እንዳልሆነ ለዓለም ማሳየት ይኖርብናል" - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

Eid Al-Fitr in Ethiopia

Eid Al-Fitr in Ethiopia. Source: Getty

በመከበር ላይ ያለውን የ1442ኛውን የኢድ አልፈጥር በዓል አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ግንቦት 4, 2013 ባስተላለፉት መልዕክት ከበዓሉ ታላቅነት ጋር አሰናስለው ወቅታዊውን የኢትዮጵያ ሁኔታ አመላክተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የዘንድሮውን ዒድ አል ፈጥር የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ በርካታ ፈተናዎች እንደተደቀኑባት እያስታወስን ነው። ክፉውን ጊዜ እንደ ዒድ ሶላት ሰብሰብ ብለን ልንጋፈጠው፣ የአንድነታችንን ልክ አሳይተን ልናልፍ ይገባል። በኅብረታችን የሚገጥሙንን ፈተናዎች እንደ ምንሻገራቸው ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያውያን እድል በእኛው እንጂ በሌላ በማንም እጅ እንዳልሆነ ለዓለም ማሳየት ይኖርብናል” ሲሉ በመልዕክታቸው ላይ አፅንዖት ሰጥተዋሳስበዋል።

PM Abiy Ahmed
Abiy Ahmed, Ethiopia's prime minister. Source: Getty

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን ገጥመው ላሉት ፈተናዎች ዋነኛ አስባብ ያሏቸውን ሁለት ዐበይት ምክንያቶች ሲያስገነዘቡም “በሕዳሴ ግድብ እና ከፊታችን ባለው ምርጫ ምክንያት ሀገራችን ፈተናዎቿ በዝተው አይተናል። እነዚህ ሁለቱን ማሳካት ለእኛ ቀላል የማይባል የስኬት በሮችን እንደሚከፍቱልን እናውቃለን። ምርጫውን በስኬት ማከናወን አዲስ የዴሞክራሲ ምዕራፍ እንደሚከፍትልን ግልጽ ነው። የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅም ግዙፍ የብልጽግና ፋና እንደሚለኩስልን ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ያውቃል” ብለዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንም በበኩላቸው በዓሉን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት “መልካም አጋጣሚዎችን ተከትሎ በተለያዩ ጊዜያት በተዘጋጁ የኢፍጠር መርሃ ግብሮች ላይ ልዩነቶቻችን ሳይገድቡን ማዕድ የተጋራንባቸው መድረኮች የአብሮነታችን ውሃ ልክ ትክክለኛ ማሳያዎች ነበሩ” በማለት መልካም ልባዊ መልዕክታቸውን ለሕዝበ ሙስሊሙ አስተላልፈዋል።

Demeke Mekonnen
Ethiopian deputy prime minister and Foreign Minister Demeke Mekonnen. Getty Source: Getty

በሌላም በኩል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ በመላው ኢትዮጵያና በየክፍለ ዓለማቱ ለሚሀኙ ሙስሊሞች በሙሉ 1442ኛውን ኢድ አልፈጥር በሐሴት የተመላ እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።

Hajji Mufti Omar Idris
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council (EIASC) head Hajji Mufti Omar Idris. Source: Getty

አክለውም ስለ ሰላም አስፈላጊነትና የአንድነትን ጠቀሜታ ልብ አሰኝተዋል። ለድሆች ማብላት፣ ሕመምተኞችን መጠየቅና ድሆችን መርዳት ሃይማኖታዊ ተግባራት መሆናቸውን አሳስበዋል።


2 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now