በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐግብር ተከናወነ

*** "ለአንድነት፣ ለሰላም እና ለፍቅር እንድትቆሙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን አደራ እላለሁ" - የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

የሰላም ፣ የአንድነት፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ መገለጫ መሆኑ የተገለፀው ኢፍጣር መርሐግብር በመስቀል አደባባይ በደማቅ ሁኔታ ተካሄዷል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ በመርኃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት "ይህ የዛሬ ኢፍጣር በሃገራችን ከዚህ ቀደም ያልታየ ስለሆነ በጣም ደስ የሚል ዝግጅት ነው። ለአንድነት፣ ለሰላም እና ለፍቅር እንድትቆሙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን አደራ እላለሁ" ብለዋል፡፡
Eid
Source: SM
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ " ሃይማኖታዊ ስርዓቶች የሁላችንም ሃብቶች ናቸው  ተአቶ  ሁላችንም ልንጠብቃቸው ይገባል። ፕሮግራሙ ባለመናበብ ምክንያት ሳይካሄድ ቢቀርም ዛሬ ባማረ መልኩ ለመካሄድ በቅቷል ነው። በመዲናችን በቀላሉ እሳት መጫር ይቻላል ብለው ለሚያስቡ አካላት እንደማይሳካ የሃይማኖት አባቶች አሳይተዋል" ሲሉ ገልጸዋል፡፡


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐግብር ተከናወነ | SBS Amharic