SKIP TO MAIN CONTENT

ጥምቀት በጎንደር በድምቀት ተከብሯል

*** "ጥምቀትን ስናከብር የኢትዮጵያ አንድነትን በማጠናከር ሊሆን ይገባል" - የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር

Gonder
Source: Demeke Kebede

1 min read

Published

By Demeke Kebede


Skip to article content

የጎንደር ከንቲባ አቶ ሞላ መልካሙ፤ ጎንደር የቱሪዝም መዳረሻዋን ከተማ የበለጠ ውበትና ድምቀት የሆነውን ጥምቀት ወደፊትም ከዚህ በበለጠ ውብና ደማቅ የቱሪስቱም መደሰቻ  እንዲሆን እንሰራለን ብለዋል።

Gonder
Source: Demeke Kebede

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ጥምቀትን ስናከብር የኢትዮጵያ አንድነትን በማጠናከር ሊሆን ይገባል ብለዋል።

አቶ አገኘሁ እንዳሉት በአምናው ጥምቀት አከባበር ባጋጠመው የደረጃ መደርመስ ለህልፈት የተዳረጉትን ፣ በዚህ ዓመቱ የህግ ማስከበር ዘመቻ ህይወታቸው ያለፉትን፣ እንዲሁም በማንነታቸው ምክንያት ለመፈናቀልና ለሞት የተዳረጉትን ወገኖቻችንን ልናስባቸው ይገባል።

 

የአርባ አራቱ አድባራት ታቦታት በጎንደር ቅዱስ ፋሲለደስ ጥምቀተ ባሕር አድረው ዛሬ በድምቀት በምዕመኑ ታጅበው ወደየ አጥቢያ ቤተክርስትያናቱ ተሸኝተዋል።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now