ሙሉ ክትባት የተከተቡ አውስትራሊያውያን ልዩ ፈቃድ ሳይጠይቁ ወደ ውጭ አገር መሔድና መመለስ እንዲችሉ ተፈቀደ

*** ሲንጋፖር ከኖቬምበር 8 ጀምሮ ሙሉ የኮሮናቫይረስ ክትባት የተከተቡ አውስትራሊያውያን ወሸባ የመግባት ግዴታ ሳይኖርባቸው ሲንጋፖርን መጎብኘት እንዲችሉ መፍቀዷን አስታወቀች።

COVID-19 update

Source: Qantas

ሙሉ የኮሮናቫይረስ ክትባት የተከተቡ አውስትራሊያውያን ለልዩ ይለፍ ፈቃድ ሳያመልክቱ ወደ ውጭ አገር መሔድና መመለስ እንዲችሉ ተፈቀደ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ከኖቬምቨር 1 ጀምሮ የልዩ ፈቃድ ጥየቃ እንደሚያበቃ አረጋግጠዋል።

ይህንኑ አስመልክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አውስትራሊያ በፈንታዋ ሙሉ ክትባት የተከተቡ ሲናፖራውያን ወደ አውስትራሊያ እንዲመጡ ለመፍቀድ መቃረቧንና ከአንድ ሚሊየን ተኩል በላይ አውስትራሊያውያን ዓለም አቀፍ የክትባት ምስክር ወረቀትን ተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው ላይ የጫኑ መሆኑን ተናግረዋል። 

የጤና ሚኒስትር ግሬግ ሃንትም በበኩላቸው፤ አውስትራሊያውያን ወደ ባሕር ማዶ ሲጓዙ ዕውቅና ያለው ሁለት ዙር ክትባት መከተባቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ሊይዙ እንደሚገባና የሁለተኛ ዙር ክትባታቸውን ሊከተቡ የሚገባውም ቢያንስ ወደ ውጭ አገር ለመሔድ ከመነሳታቸው አንድ ሳምንት በፊት መሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። 

 






 



 




Share

Published

Updated

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service