የኃዘን መግለጫ ከዓለም አቀፍ የአማራ ኅብረት

ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት(Global Amhara Coalition) በዕውቁ የስነፅሁፍ ፣ ቋንቋና ታሪክ ሊቅ በፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ህልፈተ ህይወት ምክንያት የተሰማውን ጥልቅና መሪር ሀዘን ይገልፃል።

Prof Getachew Haile.

Prof Getachew Haile. Source: G.Haile

ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ወደር ከማይገኝላቸው በጣት ከሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ውስጥ አንዱ ነበሩ:: ከሰባት አስርተ አመታት በላይ በግዕዝ ቋንቋ ምርምርና ትርጉም ፤ በገዳማትና በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ጥልቅ የሆነ ምርምር በማካሄድ ብዙ መፃህፍትንና የምርምር ፅሁፎችን ለትውልድ አበርክተዋል:: ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ወደር የማይገኝላቸው የታሪክ ሊቅ ብቻ ሳይሆኑ ለሀገራቸው አርበኛም ነበሩ::

ከምርምር ስራቸው ባልተናነሰ ኢትዮጵያ የተሻለ ስርአተ መንግስት እንዲኖራት በተደረጉት እልህ አስጨራሺ ጥረቶች ሁሉ ከግምባር በመሆን አቅጣጫ በማመላከትና በማስተባበር እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ የላቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል:: ፕ/ር ጌታቸው እጅግ ለሚወዷት አገራቸው ኢትዮጵያና ለትውልድ ያስተላለፉት ቅርስ በጣም ጥልቅና በርካታ ነው:: እርሳቸው ከሚጠበቅባቸው በላይ አበርክተው አልፈዋል::

ዋናው ጥያቄ የአሁኑና መጪው ትውልድ ይህንን የእርሳቸውን አደራ ተቀብሎ አርያቸውን ተከትሎ አገርንና ታሪክን በአግባቡ የመጠበቅና ለትውልድ የማስተላለፍ ኃላፊነት በብቃት የመወጣት መሆን ይኖርብታል ብሎ ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት በፅኑ ያምናል:: የፕሮፌሰር ጌታቸው እውቅ ስራወችም በትውልዱ እንዲሰርፁና እንዲዘከሩ ህብረቱ የበኩሉን ጥረት ያደርጋል::

በተለይ በአሁኑ ወቅት የአገራችን ጥንተ ታሪክ እኩይ በሆኑ የፓለቲካ ኃይሎች በሀሰት ትርክት እየተበረዘ ባለበት አስጊ ሁኔታ የፕሮፌሰር ጌታቸውና መሰል እውነተኛ ምንጮች በመጠቀም የቀረቡ ስራወች ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ተፈላጊነታቸው የጎላ ነዉ:: ከዚህም የተነሳ ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት የኢትዮጵያም ሆነ የአማራው ታሪክና ስልጣኔ በተገቢው ሁኔታ ትውልድ እንዲያውቀው ፤ እንዲጠብቀውና: ለመጪው ትውልድም ማስተላለፍ እንዲችል የሚያግዝ ስራ መጀመር ብቻ ሳይሆን በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥልበት ቃል ይገባል::

ይህን በማድረግ ፕ/ር ጌታቸው ለትውልዱ ያስተላለፉትን አደራ ለመወጣት የበኩሉን ድርሻ በመወጣት ምሳሌ ይሆናል:: በእውነት ኢትዮጵያ ትልቅ ሰው ፣ትልቅ ሊቅ አጣች:: ስራወቻቸው ግን ህያው ሆነው በትውልድ ሲዘከሩ ይኖራሉ:: ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት ለፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ቤተሰቦች፣ ጏደኞች፣ የስራ ባልደረቦችና: ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መፅናናትን ይመኛል::

ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ያኑርልን:: ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት (Global Amhara Coalition)


Share

Published


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service