ሲድኒ ላይ ከዛሬ ቅዳሜ አመሻሽ እስከ ጁላይ 9 ጸንቶ የሚቆይ የኮሮናቫይረስ ገደቦች ተጣሉ

*** ከእሑድ ጁን 27 ከምሽቱ 11:59pm ጀምሮ የሠርግ ሥነ ሥር ዓት ማካሔድ አይቻልም።

NSW Premier Gladys Berejiklian

NSW Premier Gladys Berejiklian speaks to the media during a press conference in Sydney, Saturday, June 26, 2021. Source: AAP

ከዛሬ ከምሽቱ 6pm ጀምሮ እስከ ጁላይ 9 እኩለ ለሊት ድረስ ጸንቶ የሚቆይ የኮሮናቫይረስ ገደቦች በመላ ሲድኒ ከተማ፣ ብሉ ማውንቴንስ፣ ማዕከላዊ ኮስትና ዎሎንጎግ ላይ ተጥሏል።

ገደቡ ሪጂናል ኒው ሳዝ ዌይልስንም ያካትታል።

ለሁለት ሳምንት የሚቆየው ገደብ የተጣለው የኒው ሳውዝ ዌይልስ ካቢኔ አስቸኳይ የቀውስ ስብሰባ ካካሔደ በኋላ ነው።

ዓርብ ዕለት የተገለጠውን የ17 ሰዎች በቫይረሱ መጠቃት ጨምሮ ባለፉት 24 ሰዓታት 29 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። 

ገደቡን ተከትሎ ከቤት ለመውጣት የሚቻለው ለገበያ ሸመታና ግልጋሎቶች፣ የሕክምና ክብካቤ፣ ለኮሮናቫይረስ ክትባት፣ አካላዊ እንቅስቃሴ ለማድረግ (በቡድን ከ10 ሰዎች ያልበለጡ) ከቤት ሆኖ ለመሥራት ወይም ለመማር ለማያስችሉ አስፈላጊ ለሆኑ ሥራዎችና ትምህርት ይሆናል። 

ከእሑድ ጁን 27 ከምሽቱ 11:59pm ጀምሮ የሠርግ ሥነ ሥር ዓት ማካሔድ የማይቻል ሲሆን፤ ቀብር ላይ ለአንድ ሰው በአራት ስኩየር ሜትር በተወሰነ ርቀት ከ100 ያልበለጡ ለቀስተኞች ሊታደሙ ይችላሉ። በቤት ውስጥ የፊት ጭምብል ማጥለቅን ግድ ይላል። 

የማኅበረሰብ ስፖርት የተጣሉት ገደቦች እስኪነሱ አይካሄድም። 

ሕጻናት ጨምሮ ቤተሰብን ለመጎብኘት ቁጥራቸው ከአምስት መብለጥ አይችልም። ከመኖሪያ ቤት ውጪ መሥሪያ ቤቶችን ጨምሮ በውጪ የሚካሔዱ ኩነቶችን አክሎ የፊት ጭምብል ማጥለቅ ግዴታ ይሆናል። 

 


Share

Published

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service