ወደ አገር ቤት ለሚመጡ አንድ ሚሊዮን የባሕር ማዶ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ አየር መንገድንና ሆቴሎች 30 በመቶ ቅናሽ እንደሚያደርጉ የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ

*** የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑም በቱሪዝም ኮሚሽን በኩል ተገልጧል።

Ethiopia's Minister of Tourism Nasise Challi

Ethiopia's Minister of Tourism Nasise Challi. Source: Getty

ወደ አገር ቤት ለሚመጡ አንድ ሚሊዮን ዲያስፖራዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድን እና ሆቴሎች 30 በመቶ ቅናሽ እንደሚያደርጉ የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ

ዓለም አቀፍ ጫናውን ለመቀነስና የኢትዮጵያን በተለይም የአዲስ አበባን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማሳየትና በዚያውም የውጭ ምንዛሬ ድጋፍ ለማስገኘት ዓላማ ያደረገ የ”አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ አገር ቤት” ጥሪ በኢትዮጵያ መንግስት መተላለፉ ይታወቃል፡፡

ይህንን ጥሪ ተክትሎ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የቱሪዝም ሚኒስትሯ አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት በተለያዩ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ ድምጽ ሆነው አገራቸውን እየደገፉ ነው ብለዋል፡፡

ከታህሳስ ወር ጀምሮ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የቀረበውን አገራዊ ጥሪ ተቀብለው ወደ አገር ቤት ይመጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና ለዚህም የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶች ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የቱሪዝም ዘርፍ ባለድርሻ ጋር በተደረገው ውይይትም የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በአዲስ አበባና በክልሎች የሚገኙ ሆቴሎች፣ አስጎብኚ ድርጅቶች እና አስጎብኚዎች እስከ 30 በመቶ የሚደርስ የአገልግሎት ቅናሽ ለማድረግ መስማማታቸውነን ሚኒስትሯ ገልፀዋል፡፡

(ደመቀ ከበደ - አዲስ አበባ)


Share

Published

Updated

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ወደ አገር ቤት ለሚመጡ አንድ ሚሊዮን የባሕር ማዶ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ አየር መንገድንና ሆቴሎች 30 በመቶ ቅናሽ እንደሚያደርጉ የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ | SBS Amharic