SKIP TO MAIN CONTENT

ወደ አገር ቤት ለሚመጡ አንድ ሚሊዮን የባሕር ማዶ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ አየር መንገድንና ሆቴሎች 30 በመቶ ቅናሽ እንደሚያደርጉ የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ

*** የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑም በቱሪዝም ኮሚሽን በኩል ተገልጧል።

Ethiopia's Minister of Tourism Nasise Challi
Ethiopia's Minister of Tourism Nasise Challi. Source: Getty

1 min read

Published

Updated

By Demeke Kebede


Skip to article content

ወደ አገር ቤት ለሚመጡ አንድ ሚሊዮን ዲያስፖራዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድን እና ሆቴሎች 30 በመቶ ቅናሽ እንደሚያደርጉ የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ

ዓለም አቀፍ ጫናውን ለመቀነስና የኢትዮጵያን በተለይም የአዲስ አበባን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማሳየትና በዚያውም የውጭ ምንዛሬ ድጋፍ ለማስገኘት ዓላማ ያደረገ የ”አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ አገር ቤት” ጥሪ በኢትዮጵያ መንግስት መተላለፉ ይታወቃል፡፡

ይህንን ጥሪ ተክትሎ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የቱሪዝም ሚኒስትሯ አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት በተለያዩ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ ድምጽ ሆነው አገራቸውን እየደገፉ ነው ብለዋል፡፡

ከታህሳስ ወር ጀምሮ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የቀረበውን አገራዊ ጥሪ ተቀብለው ወደ አገር ቤት ይመጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና ለዚህም የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶች ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የቱሪዝም ዘርፍ ባለድርሻ ጋር በተደረገው ውይይትም የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በአዲስ አበባና በክልሎች የሚገኙ ሆቴሎች፣ አስጎብኚ ድርጅቶች እና አስጎብኚዎች እስከ 30 በመቶ የሚደርስ የአገልግሎት ቅናሽ ለማድረግ መስማማታቸውነን ሚኒስትሯ ገልፀዋል፡፡

(ደመቀ ከበደ - አዲስ አበባ)


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now