በአውስትራሊያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከ153ሺ ዶላር በላይ ለገሱ

*** የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጄንሲ ምስጋና አቅርቧል

Community

Source: EDA

በአውስትራሊያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመው ሴቭ ኢትዮጵያ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ እንዲሆን በመላው አስስትራሊያ ነዋሪ ከሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ያሰባሰበውን ከ153ሺ ዶላር በላይ ወይም ከ7.6 ሚሊዮን ብር በላይ ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ አስረከበ።

ድጋፉን በሚያስረክቡበት ወቅት የማህበሩ አባላት ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ድጋፍ ከአንድ መድረክ የተሰባሰበ ሀብት መሆኑን ገልጸው፣ በቀጣይም በአውስትራሊያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በቋሚነት ከገቢያቸው ሀገራቸውን መደገፍ የሚችሉበት ሁኔታ እየተመቻቸ መሆኑን ገልጸዋል።

ድጋፉን የተረከቡት የኤጀንሲው ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሐመድ እንድሪስም በበኩላቸው በአውስትራሊያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው በመምጣታቸው እንዲሁም ከፍተኛ መጠን ያለው ሃብት በማሰባሰባቸው ምስጋናቸውን ገልጸዋል። አክለውም ዳያስፖራዎቹ በየወሩ በመደበኛነት በሚደረግ መዋጮ በቋሚነት ሀገራቸውን ለመደገፍ የጀመሩት እንቅስቃሴ በሌሎች አካባቢዎችም ሊስፋፋ የሚገባ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ዲያስፖራ ኤጀንሲ


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service