"ቧልት ነው" ቻይና ለአውስትራሊያ የአጸፋ ምላሽ ሰጠች

አውስትራሊያ የኮሮናቫይረስ መነሻ ላይ ሉላዊ ምርመራ እንዲካሔድ ከግብቦሽ ላይ መደረሱ የአውስትራሊያን አቋም ፅናት ያሳያል በማለቷ ከቻይና ስል የአጸፋ ምላሽ ገጥሟታል።

中國官方《環球時報》聲稱,澳洲正加強針對北京的間諜活動,派出特工前往中國。

File photo Source: AAP

አውስትራሊያ በኮሮናቫይረስ መንስኤ ላይ ዓለም አቀፍ ምርመራ እንዲካሔድ ግንባር ቀደም ጠንካራ አቋም አሳይቻለሁ ያለችውን  ቻይና "ቧልት" ስትል አጣጣለች።

ሰኞ ምሽት በዓለም የጤና ጉባኤ ላይ የታደሙ 110 አገራት ምርመራው እንዲካሄድ በጋራ ባቀረቡት ረቂቅ ውሳኔ ላይ ቻይና የስምምነት ድጋፏን ሰጥታለች። 

የዓለም ጤና ጉባኤ በውሳኔው ላይ ወረርሽኙን ተከትሎ የተከወኑ ዓለም አቀፍ ግብረ ምላሾችን ዘመምተኛ ያልሆነ፣ ነፃና ሁሉን አቀፍ ግምገማ እንዲደረግ ወስኗል። 

የአውስትራሊያ የቫይረሱ አነሳስ ላይ ምርመራ ይካሄድ ብሎ መግፋት ከቤጂንግ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ብርቱ ለሆነ ውጥረት ዳርጎታል። 

በአውስትራሊያ የቻይና አምባሳደር በዛሬው ዕለት ባወጡት መግለጫ የዓለም ጤና ጉባኤ አውስትራሊያ ካቀረበችው ረቂቅ የምርመራ ዕሳቤ የተለየ መሆኑን ጠቁመው፤ የዓለም ጤና ጉባኤ ውሳኔን የአውስትራሊያ ማስመሰሉ "ቧልት" ነው ብለውታል።   

በሌላ በኩል የአውስትራሊያ ግብርና ሚኒስትር ዴቪድ ሊትልፕራውድ "ይህ ክስ ሳይሆን፤ 300 000 ሕይወቶችን ስለ ቀጠፈው ወረርሽኝ ግንዛቤን ለመጨበጥ ነው" ሲሉ የአውስትራሊያን የምርመራ ይካሄድ አቋም ዛሬ ረቡዕ ከቀትር በፊት ገልጠዋል። 

የዓለም ጤና ድርጅት ግምገማው በተቻለ መጠን ቀደም ብሎ እንደሚከናወን ቃል ገብቷል።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የSBS/AAP ዜናን አጣቅሰው ምርመራው እንዲካሄድ ድጋፋቸው መቸራቸውን በቲዊተር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።

'It's a joke': China hits back at Australia's claim its coronavirus investigation stance has been vindicated
Source: Donald J. Trump

ትናንት ሰኞ ማምሻውን በተካሄደው የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ ቻይና ለኮቪድ - 19 መከላከያና በምጣኔ ሃብትና ማኅበራዊ ዕድገት ለተጎዱ አገራት በተለይም ለታዳጊ አገራት ማንሰራሪያ የሚውል 2 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላርስ መመደቧን ፕሪርዚደንት ሺ አስታውቀዋል።

 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now