የአፍሪካ ኤክስፐርቶች ሚና ከፍ እንዲል ኢትዮጵያና ሱዳን ሲስማሙ ግብፅ ሃሳቡን አልተቀበለችም

*** "በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ እየተደረገ ያለው ውጊያ ከህወኃት ጋር እንጂ ከህዝቡ ጋር አይደለም" - አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

Ambassador Dina Mufti

Ambassador Dina Mufti Source: SBS Amharic

ዛሬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መደበኛ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

ቃል አቀባዩ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው መግለጫቸው እንደተናገሩት "ተቋርጦ የሰነበተው የህዳሴ ግድብ የሶስቱ አገራት ድርድር ተጀምሯል። በተፈለገው መልኩ ስምምነት ላይ አለመደረሱ እጥረት ነው። በተለይ በአፍሪካ ኤክስፐርቶች ሚና ላይ አልተስማማንም" ብለዋል።

አምባሳደር ዲና " የአፍሪካ ኤክስፐርቶች ሚና ከፍ እንዲል የተፈለገው የአፍሪካን ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ ነው በሚል ሲሆን ኢትዮጵያና ሱዳን የተስማሙ ሲሆን ግብፅ ሃሳቡን አልተቀበለችውም። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ኤክስፐርቶች ሚና ለአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ትልቅ ሚና ስላለው ነው።" ሲሉ አብራርተዋል።

በወቅታዊው የህወኃትና የማዕከላዊው መንግስት ጦርነት ጉዳይ ብዙ መረጃ ለመስጠት የተቆጠቡት ቃል አቀባዩ በደፈናው "የኢትዮጵያ ጎረቤት አገሮች በወቅታዊው ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጎን ናቸው። ኤርትራ፣ ሱዳን ፣ ደቡብ ሱዳንና ጂቡቲ የኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት የኛም ነው ሲሉ አረጋግጠዋል።" ያሉ ሲሆን ጥልቅ መረጃዎችን ከተቋቋመው ግብረ ኃይል ማግኘት ይቻላል ብለዋል ለጋዜጠኞች።

አምባሳደር ዲና " አንድ የማረጋግጥላችሁ ነገር ግን በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ እየተደረገ ያለው ውጊያ ከህወኃት ጋር እንጂ ከህዝቡ ጋር አይደለም።" ሲሉ ተናግረዋል።

ደመቀ ከበደ፡

አዲስ አበባ


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service