የአፍሪካ ኤክስፐርቶች ሚና ከፍ እንዲል ኢትዮጵያና ሱዳን ሲስማሙ ግብፅ ሃሳቡን አልተቀበለችም

*** "በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ እየተደረገ ያለው ውጊያ ከህወኃት ጋር እንጂ ከህዝቡ ጋር አይደለም" - አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

Ambassador Dina Mufti

Ambassador Dina Mufti Source: SBS Amharic

ዛሬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መደበኛ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

ቃል አቀባዩ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው መግለጫቸው እንደተናገሩት "ተቋርጦ የሰነበተው የህዳሴ ግድብ የሶስቱ አገራት ድርድር ተጀምሯል። በተፈለገው መልኩ ስምምነት ላይ አለመደረሱ እጥረት ነው። በተለይ በአፍሪካ ኤክስፐርቶች ሚና ላይ አልተስማማንም" ብለዋል።

አምባሳደር ዲና " የአፍሪካ ኤክስፐርቶች ሚና ከፍ እንዲል የተፈለገው የአፍሪካን ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ ነው በሚል ሲሆን ኢትዮጵያና ሱዳን የተስማሙ ሲሆን ግብፅ ሃሳቡን አልተቀበለችውም። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ኤክስፐርቶች ሚና ለአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ትልቅ ሚና ስላለው ነው።" ሲሉ አብራርተዋል።

በወቅታዊው የህወኃትና የማዕከላዊው መንግስት ጦርነት ጉዳይ ብዙ መረጃ ለመስጠት የተቆጠቡት ቃል አቀባዩ በደፈናው "የኢትዮጵያ ጎረቤት አገሮች በወቅታዊው ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጎን ናቸው። ኤርትራ፣ ሱዳን ፣ ደቡብ ሱዳንና ጂቡቲ የኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት የኛም ነው ሲሉ አረጋግጠዋል።" ያሉ ሲሆን ጥልቅ መረጃዎችን ከተቋቋመው ግብረ ኃይል ማግኘት ይቻላል ብለዋል ለጋዜጠኞች።

አምባሳደር ዲና " አንድ የማረጋግጥላችሁ ነገር ግን በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ እየተደረገ ያለው ውጊያ ከህወኃት ጋር እንጂ ከህዝቡ ጋር አይደለም።" ሲሉ ተናግረዋል።

ደመቀ ከበደ፡

አዲስ አበባ


1 min read

Published

By Demeke Kebede


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now