ደቡብ አውስትራሊያ ውስጥ ከኖቬምበር 19 ጀምሮ ቢያንስ ለሚቀጥሉት ስድስት ቀናት የአገልግሎት ተቋማት በሙሉ ዝግ ይሆናሉ፡፡
ይህንንም እርምጃ ተከተሎ ለ8 ቀናት የሚቀመጥ ከፊል ገደብ ይኖራል፡፡
ሁሉም ሰው በቤቱ መቀመጥ ይኖርበታል ( አስፈላጊ በሚባሉ ተቋማት ከሚሰሩት በቀር)
ከአንድ ቤተሰብ አባል አንደ ሰው ብቻ ለምግብ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን በቀን አንድ ጊዜ ወጥቶ መገብየት ይቻላል
- ትምህርት ቤቶች እና ሙአለ ህጻናት ፦ ከኖቬምበር 19 ጀምሮ ዝግ የሚሆኑ ሲሆን ፤ በመኖሪያ ቤታቸው መቆየት ለአደጋ ከሚያጋልጣቸው ተመሪዎች እና ወላጆቻቸው አስፈላጊ ተቋማት በሚባሉት ውስጥ ከሚሰሩት ልጆች በቀር ሁሉም በቤት ይቆያሉ
- ዮኒቨርሲቲዎች፦ ከኖቬምበር 19 ጀምሮ ዝግ ይሆናሉ
- በውጭ የሚደረጉ ሁሉም አይነት የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች እና ስፖርቶች ተከልክለዋል
- የአረጋውያን መጦሪያዎች እና የአካል ጉዳተኞች መንካባከቢያ ስፍራዎች ህይወታቸው ለማለፍ ጥቂት ቀናት የቀራቸውን ሰዎችን ብቻ እንዲጎበኙ ይፈቅዳሉ
- ሁሉም የምግብ እና መጠጥ አቅራቢዎች ፤ ምግብን ገዝተው የሚሄዱባቸውን ጨምሮ ሁሉም የምግብ አዳራሾች ዝግ ይሆናሉ
- በምርጫ የሚደረጉ የቀዶ ጥገና ህክምናዎች የተሸጋገሩ ሲሆን ፤ የካንሰር እና ድንገተኛ ቀዶ ጥገናዎች በተለመደው ሁኔታ ይከናወናሉ
- የገበያ መደብሮች እና የመጠጥ መሸጫዎች ክፍት እንደሆኑ ይቆያሉ
- የህክምና ተቋማት ፤ የአእምሮ ጤና አገልግሎት ሰጪዎች ፤ የእንስሳት ሃኪም ቤቶች ክፍት ይሆናሉ ፤
- የህዝብ መጓጓዣዎች ፤ አየር ማረፊያዎች ፤ ባንክ ፤ ፖስታ ቤት እና የነዳጅ ማደያዎች ክፍት እንደሆኑ ይቆያሉ ፡፡