- በየዓመቱ አውስትራሊያ ውስጥ ጉንፋን በአማካይ ለ13,500 ህሙማን ሆስፒታል መተኛትና ሲልም ከ3,000 በላይ ለሆኑ ሞቶች ሰበብ ሆኖ አለ።

2. የጉንፋን ክትባት ነፍሰ ጡር ሲቶችን ጨምሮ ለሁሉም አውስትራሊያውያን እክል አልባ ነው። ክትባቱ ይሁንታን ከማግኘቱ በፊትም በ Therapeutic Goods Administration (TGA) አስፈላጊው የምርመራ ተግባር ይካሄዳል።

3. በየዓመቱ ከአዲስ አይነት ጉንፋን ለመከላከል የጉንፋን መከላከያ ክትባት አይነት ይለወጣል።

4. የጉንፋን መከላከያ ክትባቶች ለህመም በከፍተኛ ደረጃ ተጋልጠው ላሉ የሚሰጠው በነጻ ነው። እነሱም፤
- ዕድሜያቸው 65 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆኑ፣
- ነባር ዜጎች (Aboriginal and Torres Strait Islander people) ዕድሜያቸው ከ6 ወራት እስከ 5 ወራትና ከ15 ዓመታት በላይ የሆኑ፣
- እርጉዝ ሴቶች፣ እንዲሁም
- በብርቱ ሕመም ዝርዝር ውስጥ የሚካተቱ ሰዎች ናቸው።

5. የ2016 የጉንፋን መከላከያ ክትባት ከወርሃ ኤፕሪል ጀምሮ የጠቅላላ ሕክምና ሀኪሞችና ክትባት ሰጪዎች ዘንድ ይገኛል። ስለ ጉንፋን መከላከያ ክትባት ፕሮግራም ተጨማሪ መረጃ የሚሹ ከሆነ Immunise Australia Program ድረ-ገጽን ይጎብኙ።


