የዘውድ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት አያይዘውም "የልዑል አለማየሁን ህልፈተ-ሕይወት አስመልክቶ ለተደረገው ዝክርና ጸሎተ- ፍትሃት፣ የኢትዮጵያን ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከልብ ላመሰግን እወዳለሁ። ለግማሽ ምዕት ዓመት ግድም፣ የዐጼ ቴዎድሮስ ቀጥተኛ ተወላጆችና ቤተስቦች ይሄንን ዕድል እስከዛሬ ድረስ ያላገኙ በመሆናቸው ቤተሰባዊ ሸክምና ሃዘናቸውን አቅልሎላቸዋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ለብዙ ዓመታት ያዘሉት ግዙፍ ታሪካዊ ሸክምና ጫና ቀላል አልነበረም። እግዚአብሔር የልዑል ዓለማየሁን ጸሎተ-ፍትሃትና የመታሰቢያ ዝክረ-በዓል ቤተሰቡ እንዲያይ ስለፈቀደ ምንም ነገር ለማይሳነው አምላካችን ክብረትና ምስጋና ይግባው። ለአጼ ቴዎድሮስ ቤተሰብና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንኳን ደስ አለን" ሲሉ በምስጋና የታጀበ ደስታቸውን ገልጠዋል።

Credit: Crown Council of Ethiopia

His Imperial Highness Prince Ermias Sahle-Selassie Haile-Selassie, President of the Crown Council of Ethiopia. Credit: Crown Council of Ethiopia
Share

