"ትግራይን ማስራብ ይቁም!" - የትግራይ ማኅበረሰብ የተቃውሞ ሰልፈኞች

*** የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በምርጫ ወደ ስልጣን ይመለሳሉ ተብሎ በሚጠበቅበት ወቅት የአውስትራሊያ ነዋሪ የትግራይ ማኅበረሰብ አባላት ጁን 21 በመዲናይቱ ካንብራ የፌዴራል ፓርላማ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል።

Protesters

Protesters. Source: SBS

ላለፉት ሰባት ወራት ወሲባዊ ጥቃትና ረሃብ በጦር መሣሪያነት እንደዋሉ የገለጡት ሰልፈኞች፤ የአውስትራሊያ መንግሥት ብርቱ እርምጃ እንዲወስድ አሳስበዋል። 

"ትግራይን ማስራብ ይቁም!" ሲሉም በመፈክሮቻቸው አስተጋብተዋል።

ከተቃውሞ ሰልፈኞቹ አንዷ የሆኑት ሳሮን ብርሃን "እንደ ማኅበረሰብ ማየት የምንሻው አውስትራሊያ በንቃትና በግልጽ ወጥታ ጦርነቱን እንድታወግዝና ኢትዮጵያን ተጠያቂ እንድታደርግ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።  

በዕለቱ በሥፍራው የተገኙት የምክር ቤት አባል ፒተር ክሃሊል አውስትራሊያ እንደ ዩናይትድ ስቴትስ የቪዛ ዕቀባ አለመጣሏን አንስተው "እንደ መካከለኛ ኃይልና ከዓለም አንዷ አንጋፋ ዲሞክራሲያዊት አገር እንደመሆኗ፤ አውስትራሊያ ተሳትፎ የማድረግና ግጭቶችን የመፍታት ኃላፊነት አለባት" ብለዋል። 

በፓርላማ ግድግዳዎች ላይም ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ግጭት የሚያሳይ አንድ የምስል ኤግዚቪሽን ለዕይታ በቅቷል።

በ2012 ወደ አውስትራሊያ የመጣው የ18 ዓመቱ ክብሮም በላይ አጎቱንና ሰባት ዘመዶቹን ያጣ መሆኑን ጠቅሶ ተጨማሪ የቤተሰብ አባላትን እንዳያጣ ከፍ ባለ ጭንቀት ውስጥ ያለ መሆኑን ተናግራል።
Kibrom Belay.
Kibrom Belay. Source: SBS
አክሎም " በኖርኩባቸው 18 ዓመታት ውስጥ ያለፉት ሰባት ወራት በእጅጉ አዋኪ ነበሩ" ብሏል።

ኤግዚቪሽኑ ያተኮረው የትግራይ ውጊያ ከጀመረበት ወርኃ ኖቬምበር አንስቶ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ለግጭቱ መነሻ ሕወሓት በፌዴራሉ የሰሜን ዕዝ ጦር ላይ ጥቃት በማድረሱ እንደሆነ ገልጧል።

በግጭቱ ጎልተው ከሚነሱት አንዱ የወሲባዊ አመፅ ጥቃት ሰለባ የሆነች ሴት ለዶቼ ዌሌ እንደገለጠችው "በእያንዳንዱ ቤት እየገቡ ወንዶቹን አስገድደው ያስወጣሉ። እኔም ቤቴ ውስጥ እንድቆይ ተደርጌያለሁ። ከዚያም አስገድደው ወሲባዊ ጥቃት ፈጸሙብኝ። ሶስት ወታደሮች ናቸው አስገድደው ወሲባዊ ጥቃት የፈጸሙብኝ" ብላለች።

በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ከድር "የኢትዮጵያና የኤርትራ ወታደሮች እኒህን ግፎች ፈጽመው የተገኙ ከሆነ ለፍትሕ ይቀርባሉ የሚል አመኔታ አለዎት?" ተብለው ከSBS ለቀረበላቸው ጥያቄ "በእርግጥም አመኔታ አለኝ። የኢትዮጵያ መንግሥት የማረሚያ እርምጃዎችን ለመውሰድ ዝግጁ ነው፤ ቃልም ገብቷል" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
SBS
Source: SBS
በትግራይ ማኅበረሰብ በኩል በሰባቱ የጦርነት ወራት ምግብ ለመሳሪያነት እንደዋለ ሲነገር፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በበኩሉ ትግራይ ውስጥ ያለው የረሃብ ሁኔታ በዓለም ላይ ከየትኛውም ሥፍራ በበለጠ አያሌ ሰዎችን ለረሃብ መዳረጉን አስታውቋል።

ይሁንና አምባሳደር ሙክታር ግና የመንግሥታቸውን አቋም በማንጸባረቅ "የኢትዮጵያ መንግሥት ረሃብን ለጦር መሣሪያነት አውሏል የሚለው ክስ ፍጹም ፖለቲካዊ ተነሳሽነት ያለውና ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ ነው" ሲሉ አሌ ብለውታል። 

በሌላም በኩል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥታቸው ትግራይን መልሶ ለማቋቋም እገዛ እያደረገ መሆኑን ገልጠዋል።

 

 

 


Share

Published

Updated

By Tys Occhiuzzi
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
"ትግራይን ማስራብ ይቁም!" - የትግራይ ማኅበረሰብ የተቃውሞ ሰልፈኞች | SBS Amharic