125ኛው የአድዋ ድል በዓል በአውስትራሊያ ተዘከረ

*** "ዳግማዊ የአድዋን ታሪክ የምንሠራበት ጊዜ አሁን ነው፤ ከኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ጎን እንድትቆሙ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ" - ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጄንሲ ዋና ዳይሬክተር

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

125ኛው የአድዋ ድል በዓል ዛሬ እሑድ ፌብሪዋሪ 28 በዙም ዌብናር ታዳሚዎች ተዘክሯል።

በዕለቱ በተዘጋጀው ዝክረ መታሰቢያ ፕሮግራም መሠረት በደቡብ አውስትራሊያ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ተወካይ አማካይነት የአጤ ምኒልክ የአድዋ ዘመቻ ክተት አዋጅ ተነቧል።

በመቀጠልም በአውስትራሊያና ኒውዝላንድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተጠባባቂ ጉዳይ አስፈጻሚ በርይሁን ደጉ በዓሉን በልዩ ሁኔታ ለመዘከር ተሳትፎ ያደረጉትን በሙሉ፤ በዕለቱ በክብር ተናጋሪ እንግዳነት የተጋበዙ ተናጋሪዎችን፤ ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጄንሲ ዋና ዳይሬክተርንና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ረዳት የታሪክ ፕሮፌሰርና የኢትዮጵያ የቅርስና ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌውን በማመስገን ፕሮግራሙን አስጀምረዋል። 
SBS Amharic
Beryihun Degu. Source: SBS Amharic
ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጄንሲ ዋና ዳይሬክተርንም በበኩላቸው፤ ከአውስትራሊያና ኒውዝላንድ የኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላት የ125ኛውን ክብረ በዓል በጋራ ለመዘከር በመጋበዛቸው ክብር የተሰማቸው መሆኑን በመግለጽ ምሥጋናቸውን አቅርበዋል።

በከብረ በዓሉ ላይ ባሰሙት ንግግር "የአድዋ ድል በአንድ ቀን ብቻ ተከብሮ የሚያልፍ አይደለም። አፍሪካውያን ሁሉ ሁሌም የሚያከብሩት ነው። ኢትዮጵያ ለዓለም ካበረከተቻቸው አያሌ በረከቶችዋ ውስጥ አንዱና ዋና የአድዋ ድል ነው። ዛሬ ሰንደቅ ዓላማችን በብዙ የአፍሪካ አገራት አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ የነፃነት ምልክት እስከሚሆን አባቶቻችን አድርሰውናል። በዚህም ልንኮራ ይገባናል። አድዋን እኛ ብቻ ሳንሆን የምናከብረው በበርካታ የአፍሪካ አገራት ዩኒቨርሲቲዎች ይህን እያከበሩ ናቸው" ብለዋል።
SBS Amharic
Selamawit Dawit. Source: SBS Amharic
አያይዘውም "የዳግማዊ አድዋን ታሪክ የምንሠራበት ጊዜ አሁን ነው" በማለት "ከኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ጎን እንድትቆሙ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ" ሲሉ ጥሪያቸውን ለማኅበረሰቡ አባላት አቅርበዋል።    

ሌላው የክብረ በዓሉ ተጋባዥ ተናጋሪ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ረዳት የታሪክ ፕሮፌሰርና የኢትዮጵያ የቅርስና ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው "የአድዋ ድል፤ መንስኤ፣ ሂደትና ውጤት" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሁፋቸውን አቅርበዋል።
SBS Amharic
Asst Prof Abebaw Ayalew. Source: SBS Amharic
በዝክረ መታሰቢያው ላይ አገር አዳሙ፣ ሰፋኒት መንግሥቱና ዲያቆን ምኒልክ ዓለሙ ለአድዋ ታላቅነት መዘከሪያ ያቀረቧቸው የስንኝ ቋጠሮዎች ልዩ ዝግጅቱን ሞገስ አላብሷል።

የታሪክ ረዳት ፕሮፌሰር አበባው ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ ላይ በዝግጅቱ የውይይት መድረክ ከታዳሚዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶበታል። 

 

በገለጣቸውም ወቅት "ይህ ታላቅ ለ125ኛ ጊዜ ሲከበርና ሲዘከር የጦርነቱን መንስኤዎች፣ የኢትዮጵያውያንን የዲፕሎማሲ ትግል፣ ኢትዮጵያውያን ጀግኖች ለነፃነት የከፈሉትን መስዋዕትነት፣ የድሉን ትሩፋቶችና ብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ ፋይዳዎች ለዘመናችን ትውልድ በሚገባ ማስገንዘብ በእጅጉ አስፈላጊ ነው" ብለዋል።  

በማጠቃለያቸውም "በውጭ አገር የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን በአገር ቤት ላሉ ኢትዮጵያውያን አርአያ እንድትሆኑ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ" ብለዋል።

 


Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
125ኛው የአድዋ ድል በዓል በአውስትራሊያ ተዘከረ | SBS Amharic