SKIP TO MAIN CONTENT

የኒያ ፋውንዴሽንና የጆይ ኦቲዝም ማዕከል መስራች ዘሚ የኑስ በኮቪድ 19 ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

*** ወ/ሮ ዘሚ በኮቪድ 19 ቫይረስ ተይዘው በፅኑ ህሙማን መከታተያ ሳሉ “በፀሎት አስቡኝ” ብለው ነበር።

Zemi Yunus
Zemi Yunus. Source: JOY Center of Excellence for Autism

1 min read

Published

By Demeke Kebede


Skip to article content

የጆይ ኦቲዝም ማዕከል መስራችና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዘሚ የኑስ፣ በኮቪድ 19 ቫይረስ ተይዘው በፅኑ ህሙማን መከታተያ ውስጥ የነበሩ ሲሆን፣ “በፀሎት አስቡኝ” የሚል መልዕክትን ከቀናቶች በፊት አስተላልፈው ነበር።

አንደኛው ወንድ ልጃቸው የኦቲዝም ተጠቂ (የአዕምሮ እድገት እክል ያለበት ) መሆኑን ተከትሎ ስለችግሩ በጥልቀት እንዲረዱና ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች መፍትሔ ለማስገኘት በብዙ የደከሙ ሰው ነበሩ።

የኦቲዝም ታማሚ ልጃቸው ጆጆን ለማሳደግ የተጋፈጡትን ከባድ ሕይወት በአደባባይ በመናገርና ለዘመናት ከህመሙ ጋር ተያይዞ የነበረውን አጉል እምነትና ዝምታ በመስበር ለብዙ ወገኖች ደራሽ የሆኑት ፋና ወጊዋ ወ/ሮ ዘሚ የኑስ፣ በኮሮ ቫይረስ የተነሳ ሕይወታቸውን አጥተዋል።

የኒያ ፋውንዴሽን ጆይ የኦቲዝም ማዕከል በአሁኑ ወቅት ከ 80 በላይ የኦቲስቲክ ልጆችን ያቀፈ ሲሆን፣ ከተቋቋመ ከ19 ዓመታት በላይ አስቆጥሯል።

ዛሬ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ሳር ቤት አካባቢ በሚገኘው ኒያ ፋውንዴሽን ዘሚ የክብር አሸኛኘት እንደሚደረግና ስርዓተ ቀብራቸው እንደሚፈፀም ተገልጿል።

[ ደመቀ  ከበደ - አዲስ አበባ ]


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now