ከአውስትራሊያ የበጋ ደን ቃጠሎዎች የዘንድሮው የከፋ በመሆኑ 10.7 ሚሊየን ሄክታርስ ያህል ጋይቷል፣ 2,204 መኖሪያ ቤቶች ወድመዋል፣ እስከ ጃኑዋሪ 11, 2020 ድረስ የ29 ሰዎች ሕይወቶች ተቀጥፏል፣ ከአንድ ቢሊየን በላይ እንሰሳት ለሞት ተዳርገዋል። አውስትራሊያውያንም ፈጣን ለጋስ የእርዳታ እጆቻቸውን በእሳት ቃጠሎው ለተጎዱት ማኅበረሰብ አባላት ማቋቋሚያ እየዘረጉ ነው። የኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን ማኅበረሰብ አባላትም በጋራ ለመቸር ተነሳስተዋል። ይህንኑ አስመልክተን ከአቶ ተስፋዬ እንደሻው - የቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፣ አቶ ኃይለ ልዑል ገብረ ሥላሴ - የአፍሪካ ቲንክ ታንክ ሊቀመንበርና አቶ ዓለማየሁ በዛብህ - የቀድሞው የቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፀሐፊ ጋር ተወያይተናል።
Share






