“በደን ቃጠሎ ለደረሱት አደጋዎች በአንድነት ኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያንነታችንን የሚያስመሰክር እርዳታ እናድርግ” - የማኅበረሰብ መሪዎች

Tesfaye Endeshaw, Haileluel Gebreselassie, Alemayehu Bezabih Source: Courtesy of TE, HLGS, and AB
ከአውስትራሊያ የበጋ ደን ቃጠሎዎች የዘንድሮው የከፋ በመሆኑ 10.7 ሚሊየን ሄክታርስ ያህል ጋይቷል፣ 2,204 መኖሪያ ቤቶች ወድመዋል፣ እስከ ጃኑዋሪ 11, 2020 ድረስ የ29 ሰዎች ሕይወቶች ተቀጥፏል፣ ከአንድ ቢሊየን በላይ እንሰሳት ለሞት ተዳርገዋል። አውስትራሊያውያንም ፈጣን ለጋስ የእርዳታ እጆቻቸውን በእሳት ቃጠሎው ለተጎዱት ማኅበረሰብ አባላት ማቋቋሚያ እየዘረጉ ነው። የኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን ማኅበረሰብ አባላትም በጋራ ለመቸር ተነሳስተዋል። ይህንኑ አስመልክተን ከአቶ ተስፋዬ እንደሻው - የቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፣ አቶ ኃይለ ልዑል ገብረ ሥላሴ - የአፍሪካ ቲንክ ታንክ ሊቀመንበርና አቶ ዓለማየሁ በዛብህ - የቀድሞው የቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፀሐፊ ጋር ተወያይተናል።
Share




