የአውስትራሊያ ነባር ዜጎች ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅናን አግኝተው ቋሚ የድምፅ ለፓርላማ አማካሪ አካል ለማቆም ቅዳሜ ኦክቶበር 14 / ጥቅምት 3 ይሁንታን ለመስጠት ወይም ለመንፈግ አገር አቀፍ ሕዝበ ውሳኔ ይካሔዳል። ኢትዮጵያውያም - አውስትራሊያውያንም በ 'ይሁን ' ወይም 'አይሁን ' ግለ ውሳኔ የሕዝበ ውሳኔ ድምፃቸውን ይሰጣሉ። ወ/ሮ አዲስ ዓለም ፀጋዬ ከኩዊንስላንድ፣ አቶ ጥላዬ ተከተል ከደቡብ አውስትራሊያና ነርስ ሰላም ተገኝ ከምዕራብ አውስትራሊያ የድምፅ ለፓርላማ አተያየትና የሕዝበ ውሳኔ ድምፃቸውን እንደምን ለመስጠት እንደወሰኑ ይናገራሉ።
አንኳሮች
- የድምፅ ለፓርላማ ፋይዳዎች
- የይሁን፣ አይሁንና ገና አልወሰንኩም አተያዮች
- የሕዝበ ውሳኔ ቀን
Share






