ዶ/ር ዮናታን ድንቁ - በአውስትራሊያ ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ እና ዶ/ር ደሴ ታርቆ - በአደላይድ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ፤ የ2026 የአውስትራሊያ ዓመታዊ የፌዴራል በጀት ትሩፋቶችንና እንከኖችን ነቅሰው ያመላክታሉ።
አንኳሮች
- ጥቅል አተያይ
- የኑሮ ውድነት
- የምጣኔ ሀብት ስክነት
- የውጭ አሉታዊ ተፅዕኖዎች ጎጂ ጎኖች
የዘንድሮው በጀት፤ ከአሁን በፊት በቀጥታ ይደረጉ የነበሩ የኑሮ ውድነትን ሊያለዝቡ የሚችሉ ዓይነት እርምጃዎችን ያየሁበት በጀት አይደለም። በዓይነቱ ለየት ያለ ነው። ከምጣኔ ሀብት የኑሮ ሸክም ጋር የሚመጣጠን ነው ብዬ በግሌ አላስብም።ዶ/ር ዮናታን ድንቁ፤ በአውስትራሊያ ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ
በጀቱ አንዱ ትኩረቱን ያደረገው ግብር ቅነሳ ላይ ነው። ሌሎችም የድጎማ ማሻሻያዎች ተካሂደዋል። ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎችን፣ ሥራ የሌላቸውን፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ሰዎችና ተማሪዎችን የመሳሰሉ የሕብረተሰብ ክፍሎች ያላገናዘበ ነው። በበጀቱ ተጠቃሚዎች አሉ። ተጎጂዎችም አሉ።ዶ/ር ደሴ ታርቆ፤ በአደላይድ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ
Share






