ፀጋአብ ክበበው፤ በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን ተሰናባች አምባሳደር ናቸው። ሰሞኑን በጄኔቫ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ተመድበዋል። ስንብታቸውን አስባብ በማድረግም በአጭሩ የስድስት ወራት ቆይታቸው ከአውስትራሊያ መንግሥት፣ ኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን ማኅበረሰብ አባላትና አውስትራሊያውያን ጋር ስለነበራቸው የሥራ ትብብርና ኤምባሲው ስለሚሰጣቸው አገልግሎቶች ይናገራሉ።
አንኳሮች
- የኢትዮጵያ - አውስትራሊያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
- ማኅበረሰባዊ አገልግሎቶች
- ስንብት
Share






