የመደመር የውይይት መድረክ በሜልበርና ሲድኒ

Beryihun Degu Source: SBS Amharic
አቶ በሪሁን ደጉ፤ በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የዳያስፖራ ጉዳዮች ኃላፊ፤ ቅዳሜ ፌብሪዋሪ 2, 2020 በሜልበርን፤ እሑድ ፌብሪዋሪ 23, 2020 ሲድኒ በ “መደመር” ፅንሰ ሃሳብ ላይ ስለሚካሄደው ሕዝባዊ ውይይት ይናገራሉ። በእለቱም በሁለቱም ከተሞች አቶ መሐመድ ራፊ አባራያ - በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ተንታኝና አቶ ዮናስ ዘውዴ - በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የ PhD ተማሪና በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ተጠባቢ በመደመር መጽሐፍ ጭብጥ ዙሪያ ግንዛቤ ያስጨብጣሉ።
Share




