ቪክቶሪያ የሚገኘው ዲኪን ዩኒቨርሲቲ ሕፃናትና ወላጆች ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ቁሶች ጋር ምን ያህል ጊዜያትን እንደሚያሳልፉ ጥናታዊ ዳሰሳ ለማድረግ ኢትዮጵያውያን ወላጆችን መጋበዙን፤ ዶ/ር ተበጀ ሞላ በዲኪን ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ፖሊሲና የማኅበራዊ ፍትሕ ተመራማሪና መምህር ገለጡ።
አንኳሮች
- የጥናታዊ ዳሰሳ ተሳትፎና ሂደት
- የጥናታዊ ዳሰሳ ጠቀሜታዎች
- የጥናታዊ ግኝቶች ለሕዝብ ተደራሽ መሆንና የፖሊሲ ግብዓት ፋይዳዎቹ
በጥናታዊ ዳሰሳው ለመሳተፍ ካሹ እዚህ ይጫኑ።
Share





