ቅዳሜ ኦክቶበር 14 / ጥቅምት 3 በመላ አውስትራሊያ ለአውስትራሊያ ነባር ዜጎች ቀዳሚ ባለ አገርነት ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅና ለመቸርና በተለይ እነሱን አስመልክቶ አዋኪና ጎጂ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በቋሚ አካልነት ተሰይሞ ለመንግሥት ሥራ አስፈፃሚና ፓርላማ የመፍትሔ ሃሳቦችን የሚያቀርብ ጉዳይ አስፈፃሚ አካል ለማቆም ሕዝበ ውሳኔ ይካሔዳል። ዶ/ር ይርጋ ገላው፤ በከርተን ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ትምህርት ማዕከል ገዲብ ተመራማሪና መምህር የድምፅ ለፓርላማን የሰብዓዊ መብቶች ፋይዳዎች ነቅሰው ያስረዳሉ።
አንኳሮች
- ድምፅ ለፓርላማ
- ዓለም አቀፍ የነባር ዜጎች ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ መርሆዎችና ደረጃዎች
- የድምፅ ለፓርላማ ክሽፈትና መዘዞቹ፤ ስኬትና ትሩፋቶቹ
Share






