መላክ ጸሃይ መንግስቱ ሀይሌ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያ የምስራቅ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ እንዲሁም የብሪዝበን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ፤ ሀገረ ስብከቱ የዘንድሮው የጥምቀት በአል በየአድባራቱ እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል ብለዋል። ህዝበ ክርስቲያኑ መንግስት የሚያወጣውን የኮሮናቫይረስ መመሪያዎችን በመከተል ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ እንዲያከብሩ አሳስበዋል ።
Share






