የምርጫ 2013 በስኬት መጠናቀቅ ፋይዳዎችና ለክሽፈት የመዳረግ መዘዞች ምን ሊሆኑ ይችላሉ?

Staff of the National Electoral Board of Ethiopia register people in a registration station in Addis Ababa, Ethiopia. Source: Getty
አቶ ነዓምን ዘለቀ - የቀድሞው የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር አባልና የውጭ ጉዳይ ኃላፊና ዶ/ር ዮሃንስ ገዳሙ በGeorgia Gwinnette College የፖለቲካ ሳይንስ መምህር መጪውን የኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርጫ አስመልክተው ይናገራሉ። ዶ/ር ዮሃንስ “ይህ ምርጫ ፋይዳው ትልቅ ነው። ምክንያቱም ኢትዮጵያ በሕዝብ የተመረጠ፤ ሕዝባዊ ተቀባይነት ያለው መንግሥት ይኖራታል ማለት ነው” ሲሉ፤ አቶ ነዓምን በበኩላቸው “በአብላጫ ወይም በጥምር መንግሥትነት የሚመጣው መንግሥት ሕጋዊነትና ቅቡልነት እንዲኖረው ምርጫው በጣም አሥፈላጊ ነው” ይላሉ።
Share



