እሑድ ሴፕቴምበር 18 / መስከረም 8 ከ10:00am - 5:00pm በብሪስበን ከተማ የአውስትራሊያ ሞዛይክ መድብለ ባሕል ፌስቲቫል በሮማ ስትሪት፣ ፓርክላንድ ይካሔዳል። ፌስቲቫሉ የምግብ አቅርቦትና የምግብ አበሳሰል ትዕይንቶችን አካትቶ የተለያዩ ክንዋኔዎች ይስተናገዱበታል። በባሕላዊ ምግብ ተሳታፊ የሆነው የሺ ቡና፤ ኢትዮ - አፍሪካውያን ካፌና ሬስቶራንት ባለቤት አቶ ወርቅነህ ባይህ ስለ ፌስትቫሉና የየሺ ቡና መሰናዶዎች ይናገራሉ።
Share






