አቶ ዮናስ ዘውዴ - በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የ PhD ተማሪ - በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ተጠባቢና አቶ መሐመድ ራፊ አባራያ - በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ተንታኝ በመደመር ትርጓሜ፣ የመደመር መርሆዎችና የአገር ውስጥ ፖሊሲ አቅጣጫዎች ምልከታ ላይ አተያዮቻውን ያጋራሉ። አቶ ዮናስ ዘውዴና አቶ መሐመድ ራፊ አባራያ ወደ አውስትራሊያ የመጡት ቅዳሜ ፌብሪዋሪ 2, 2020 በሜልበርን፤ እሑድ ፌብሪዋሪ 23, 2020 ሲድኒ በመደመር መጽሐፍ ፅንሰ ሃሳብ ላይ በሚካሄደው ሕዝባዊ ውይይት ለኢትዮጵያውያን ማኅበርሰብ አባላት ገለጣ ለማድረግ ነው።
Share






