የአውስትራሊያ ቀን በየዓመቱ ጃኑዋሪ 26 በመላው አገሪቱ ይከበራል። እ.ኤ.አ. ከ1788ቱ የእንግሊዞች ሲድኒ ኮቭ ሠፈራ ጋር ተያይዞ አዲሱ የአውስትራሊያ ማንነት ማክበሪያ ቀን ሆኗል። ሆኖም ዕለቷ ለአውስትራሊያ ነባር ዜጎች “ዕለተ ኃዘን፣ ዕለተ ወረራና የመቋቋሚያ ቀን” ተደርጋ ትታያለች። በየዓመቱም ሁሉም ዜጎች የእኛ የሚሉት የአውስትራሊያ ቀን በአማራጭነት እንዲሰየም ብርቱ ክርክሮች ይካሄዳሉ። በዚሁ ዕሳቤ ዙሪያ የዘንድሮው የውይይት ተሳታፊዎቻችን አቶ አበበ መኮንን ከሜልበርን - ቪክቶሪያና አቶ አበበ ሃብተስላሴ ከአደላይድ - ደቡብ አውስትራሊያ ናቸው።
Share






