ሕልሟን ትታ ሔደች፤ "ኡርጌ የሰው ልጆች መብቶች የሚያስቆጫትና የማኅበረሰባችን ማዕከል ነበረች" አቶ ያደታ ሞሲሳ

Urge Fekadu Denegde. Credit: F.Dinegde
በለጋ ዕድሜዋ በወሊድ ሳቢያ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው ኡርጌ ፈቃዱ የቀብር ሥነ ሥርዓት እሑድ ዲሴምበር 17 ቀን 2023 / ታህሳስ 7 ቀን 2016 ሜልበርን - አውስትራሊያ ይከናወናል። በሐዘንና በሰቀቀን የሚለዩዋት አባቷ አቶ ፈቃዱ ዲነግዴ "እኛ አሳደግናት እንጂ ኡርጌ የሁሉም ሰው ናት" ሲሉ፤ የቅርብ ጓደኛዋ ሰላማዊት ኡርጋ "እሷ ባለችበት ጨለማ የለም፤ ብርሃን እንጂ። በአጭር ዕድሜ ከሁላችንም በላይ ኖራለች" በማለት ገልጠዋታል።
Share