በለጋ ዕድሜዋ በወሊድ ሳቢያ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው ኡርጌ ፈቃዱ የቀብር ሥነ ሥርዓት እሑድ ዲሴምበር 17 ቀን 2023 / ታህሳስ 7 ቀን 2016 ሜልበርን - አውስትራሊያ ይከናወናል። በሐዘንና በሰቀቀን የሚለዩዋት አባቷ አቶ ፈቃዱ ዲነግዴ "እኛ አሳደግናት እንጂ ኡርጌ የሁሉም ሰው ናት" ሲሉ፤ የቅርብ ጓደኛዋ ሰላማዊት ኡርጋ "እሷ ባለችበት ጨለማ የለም፤ ብርሃን እንጂ። በአጭር ዕድሜ ከሁላችንም በላይ ኖራለች" በማለት ገልጠዋታል።
Share





