ቅዳሜ ሜይ 21 / ግንቦት 13 የሚካሔደው የአውስትራሊያ ብሔራዊ ምርጫ የውይይት መድረክ አጀንዳችን ነው። የውይይቱ ተሳታፊዎች ነርስ ኤልሳ ወልዱ - ዩናይትድ አውስትራሊያ ፓርቲን በመደገፍ፣ አቶ አበበ መኮንን - የአውስትራሊያ ግሪንስ ፓርቲን በመደገፍ፣ አቶ አያሌው ሁንዴሳ - የአውስትራሊያ ሌበር ፓርቲን በመደገፍ ድምፃቸውን ይሰጣሉ። ኢትዮጵያውያን-አውስትራሊያውያንም ለቤተሰብ፣ ለማኅበረሰብና ለአገር ጥቅም ሲሉ ለሚደግፏቸው ፓርቲዎች ድምፃቸውን እንዲሰጡ ይጠይቃሉ። የአውስትራሊያ ሊብራል ፓርቲን በመወከል ተጋብዘው የነበሩ ተሳታፊ በውይይቱ ወቅት አልተገኙም።
Share






