የዓመቱን መሰናበቻ አስባብ አድርገን ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ካስተላለፍናቸው ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶቻችን የተወሰኑትን ነቅሰንና ቀንጭበን በምልሰታዊ ምልከታ እናቀርባለን። ባለፈው ወርኃ ጃኑዋሪ ካነጋገርናቸው ውስጥ አቶ ዓለሙ ያይኔ - የኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ ሊቀመንበርና ዶ/ር ኤርሚያስ ዓለሙ - የኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ ምክትል ሊቀመንበር ይገኙበታል። የመነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳያችን የነበረው ኮሚቴው "ሱዳን በወረራ ከያዘችው የወረራ ግዛት በአስቸኳይ ለቅቃ መውጣት አለባት" ሲል ያወጣውን መግለጫ ፋይዳ አስመልክቶ ነበር።
Share






