ኤልያስ መልካ ዛሬ በሕይወት የለም። በያዝነው ወርኃ ኦክቶበር ከዚህ ዓለም ተለይቷል።ይሁንና ከሕይወት የገዘፈ ውርሰ አሻራውን በኢትዮጵያ ዘመናዊ የሙዚቃ ዓለም ውስጥ አኑሮ አልፏል። “ስም ከመቃብር በላይ ይኖራል” እንዲባል። የአርቲስት ኤልያስ መልካን ማለፊያ ሥራዎች ዋቤ በመንቀስ ኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን የኪነ ጥብበ ቤተሰብ አባላት ናቲ ማን፣ ኤልያስ የማነ፣ ሰሎሞን ሲሳይና ዘላለም ንጋቱ ዝከረ ትውስታቸውን ቸረውናል።
Share






