በ95 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የቀድሞው የዚምባቡዌ ፕሬዚደንት ሮበርት ሙጋቤ በመንግሥታዊ የቀብር ሥነ ሥርዓት ሐራሬ ላይ ሲሽኙ፤ አውስትራሊያ ውስጥ ነዋሪ በሆኑ ዚምባቡዌያውያን ዘንድ በውርሰ አሻራቸው ላይ ዝንቅ አተያዮች ተንጸባርቀዋል። በገሚሶቹ ዘንድ፤ የሙጋቤ ሞት በዘመነ ፕሬዚደንትነታቸው በፈጸሟቸው የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ተጠያቂ ሳይሆኑ ማለፍ ሆኖ ሲገልጥ፤ በሌሎች አንደበት ግና ለዚምባቡዌ ድቅቀት ጣት መጠቆሚያ ተደርገዋል የሚል አተያዮች ተሰንዝረዋል።
Share






