Life and Legacy: Emeritus Prof Bereket Habte Selassie - Pt 1

Life and Legacy: Emeritus Prof Bereket Habte Selassie - Pt 1

Emeritus Prof Bereket Habte Selassie Source: Courtesy of KTA

Habte Selassie - Pt 1 ከወ/ሮ ለተሃይማኖት ነጋሢና ቄስ/ፓስተር ሃብተስላሴ ጉልበት አብራክ የተከፈሉት ጎምቱው ፕሮፌሰር በረከት ሃብተስላሴ በአገረ አሜሪካ ‘ወርቃማ ዘመን የሚባለውን የጡረታ ሕይወታቸውን እያጣጣሙ ይገኛሉ።


የሰላ ብዕራቸውና ግና አብሯቸው አልተጠወረም። ከቶውንም በእፎእይታ ዘመናቸው እንዳይቦዝኑ ከደራሲነት ጎራ አሰልፏቸው አለ።

Life and Legacy: Emeritus Prof Bereket Habte Selassie - Pt 1
Prof Bereket Habte Selassie Source: Courtesy of Elias

በዘውዳዊው ሥርዓት ዘመን የመጀመሪያው የኢትዮጵያ አገር በቀል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የሥልጣን እርከን ላይ ደርሰዋል።

በየካቲት ፷፮ቱ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮት ወቅት የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥቱ መርማሪ ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ ነበሩ።

በኋላም ኤርትራ ሉዓላዊ አገር እንድትሆን ተጋዳላይ ሆነው ታግለዋል። ሲልም፤ የኤርትራ ሕገ መንግሥት አርቃቂ ኮሚሽን ሊቀመንበር ሆነዋል።

በረከት ሃብተስላሴ፤ ከአዲ ንፋስ የትውልድ ቀዬአቸው ተንስተው ለፊደል ቆጠራ እንደምን ወደ አሥመራ እንደአቀኑ፣ በባቡር ገስግሰው ሐረር እንደደረሱ፣ በጢያራ ከንፈው ከአዲስ አበባ ጄኔራል ዊንጌት ትምህርት ቤት ተማሪነት የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የሕግ ምሩቅነት እንደበቁ በምልሰት ያነሳሉ።

አገር ቤት ተመልሰውም ከዋና ተቆጣጣሪነት፣ ወደ ምክትል ዓቃቤ ሕግነት፣ አልፈውም ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ስለመድረሳቸውም  ያወጋሉ።

የክፍል አንድ ውይይታችንን መንደርደሪያ ያደረግነው ‘ለምን ከልጅነት ጊዜዎ አንነሳም?’ በማለት ነው።  

 


Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Listen to our podcasts

Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now