Like Father, Like Sons: Meet the former Ethiopian national football team players

Source: SBS Amharic
አቶ ወንድሙ በቀለ እ.ኢ.አ. በ1953 ዓ.ም. የመብራት ኃይል (ኤሌክትሪክ) ቡድን መሥራች ናቸው። ቡድናቸውን በተጫዋችነትና አሰልጣኝነትም አገልግለዋል፤ ሲልም ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአንደኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን ላይ ተጫውተዋል። ሁለት ወንዶች ልጆቻቸውን ኢርሚያስ ወንድሙንና ሰሎሞን ወንድሙን በእግራቸው ተክተው ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋችነት አብቅተዋል። በወርኃ ኦገስት የፊልም ዳይሬክተር ዓቢይ አየለና የእግር ኳስ አሰልጣኝ አስፋው ሳህሉ፤ የአቶ ወንድሙን አስገራሚና ድንቅ ግለ ታሪክን በዶክሜንታሪ ፊልም ቀርጸው ለአገራዊ አስተዋጽኦዎቻቸው የምሥጋና ክብርና ሞገስን አላብሰዋቸዋል።
Share




