ሹመት - ከሚኒስትር እስከ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር

ሁለቱ ተሿሚ ሚኒስትሮች የብልፅግና ፓርቲ አባላት አይደሉም

Temesgen.jpg

Temesgen Tiruneh, incoming deputy prime minister of Ethiopia. Credit: ENA

ዛሬ ሐሙስ ጥር 30 በተካሔደው 6ኛው የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 15ኛ መደበኛ ስብሰባ ከፍተኛ መንግሥታዊ የሥራ ኃላፊነቶች ተሰጥተዋል።

በሥራ ኃላፊነት አሰጣጡም፤
  • አቶ ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣
  • አምባሳደር ታዬ አፅቀ ሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣
  • ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሆነው ተሾመዋል።
ከተሿሚዎቹ ሁለቱ አምባሳደር ታዬ አፅቀ ሥላሴና ዶ/ር መቅደስ ዳባ የገዢው ብልፅግና ፓርቲ አባላት እንዳልሆኑ ተነግሯል።
Ministers.jpg
Newly appointed ministers Ambassador Taye Atseke Tselassie (L) and Dr Mekdes Daba (R). Credit: EPO

ይህንኑ አስመልክቶም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ "የብልፅግና አባል ባይሆኑም አገርና ጥቅምን ባስቀደመ መልኩ የሚደረገው መተካካት ይቀጥላል" ብለዋል።

አቶ ተመስገን ጥሩነህና አምባሳደር ታዬ አፅቀ ሥላሴ የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ኃላፊነቶችን ሊረከቡ የቻሉት በተሰናባቹ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ምትክ በመተካት ነው።
gettyimages-1235501851-612x612.jpg
Outgoing Ethiopian Deputy Prime Minister and Foreign Minister Demeke Mekonnen. Credit: KENA BETANCUR/POOL/AFP via Getty Images

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service