መቀሌ ላይ የአየር ጥቃት መድረሱ ተነገረ፤ በመንግሥት በኩል ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ አልተሰጠም

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲሱ ተመራጭ የኬንያ ፕሬዚደንት በዓለ ሲመት ላይ ለመገኘት ናይሮቢ ገቡ።

A general view of the city of Mekelle, Ethiopia.jpg

A general view of the city of Mekelle, Ethiopia, on January 5, 2020. Credit: EDUARDO SOTERAS/AFP via Getty Images

በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አዲ ሃቂ ካምፓስ ላይ በኢትዮጵያ መንግሥት የድሮን አየር ጥቃት መድረሱን የሕወሓት ቃል አቀባይና የሰላም ልዑክ ቡድን አባል አቶ ጌታቸው ረዳ አስታወቁ።

ቃል አቀባዩ የአየር ጥቃት መድረሱን የገለጡት በቲዊተር ገፃቸው ሲሆን፤ በሰውና በንብረት ላይ ስለደረሱ አደጋዎች ግና የሰጡት መረጃ የለም።

በኢትዮጵያ መንግሥት በኩልም በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ላይ ደረሰ የተባለውን የቃል አቀባዩን ገለጣ አስመልክቶ የማስተባበያም ሆነ የማረጋገጫ ቃል አልተሰጠም።

ሕወሓት መስከረም 1, 2015 ላወጣው የሰላም ድርድር ጥያቄም በመንግሥት በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም።


በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ5ኛው የኬንያ ፕሬዚደንት ዊሊያም ሩቶ በዓለ ሲመት ላይ ለመገኘት ከልዑካን ቡድን አባላቶቻቸው ጋር ናይሮቢ ገብተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዓለ ሲመቱን አስታክከው ከኡጋንዳው ፕሬዚደንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ጋር የጎንዮሽ ንግግር አካሂደዋል።

ተመራጭ ፕሬዚደንት ሩቶ በቀጣዩ አንድ ሰዓት ውስጥ ቃለ መሐላ የሚፈፅሙ ይሆናል።

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service