"በመድብለ ባሕላዊት ሀገራችን ዋጋ እና ከበሬታ በተቸራቸው የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አስተዋፅዖዎች አውስትራሊያ በልፅጋለች፤ መልካም አዲስ ዓመት!" ጠ/ሚ አንቶኒ አልባኒዚ

የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ፤ ለኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት አደረሳችሁ ሙሉ መልዕክት።

SOCCEROOS PARLIAMENT HOUSE VISIT

Australian Prime Minister Anthony Albanese at Parliament House in Canberra, Thursday, September 4, 2025. Source: AAP / LUKAS COCH/AAPIMAGE

ዕንቁጣጣሽን እያከበራችሁ ባላችሁበት ወቅት ልባዊ መልካም ምኞቴን አቀርባለሁ።

የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት የለውጥና እና ተስፋ ወቅት ነው።

ከቤተሰብ እና ወዳጆች ጋር በጋራ ለመታደም፣ አንድ ላይ ስላሰባሰባችሁም ምስጋና ማቅረቢያና በብሩህ ተስፋ ተመልቶ ወደፊት ማማተሪያ ጊዜ ነው።

በመድብለ ባሕላዊት ሀገራችን ዋጋ እና ከበሬታ በተቸራቸው የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አስተዋፅዖዎች አውስትራሊያ በልፅጋለች።

ዕንቁጣጣሽ በተለምዷዊ አጠራር አውስትራሊያን ሀገራችን ብለው በሚጠሩቱ ሁሉ በበርካታ መንገዶች ሀገራችን የተጠናከረችበት መሆኑን ልብ የሚያሰኝ ብርቱና ልብን አሟቂ ሆኖ ግዘፍ የሚነሳ ነው።

ለሁላችሁም፤ አዲሱ ዓመት የደህንነትና የሐሴት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

ሰላም፣ ብልፅና እና ደስታን ለእናንትና ለዘመድ አዝማዶቻችሁ ሁሉ ይዞላችሁ ይምጣ።

አንቶኒ አልባኒዚ

የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር

ሴፕቴምበር 2025


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now