"በፌዴራል ሌበር ስም ለሁላችሁም መልካም አዲስ ዓመትን ልመኝ እወዳለሁ" አንድሩ ጊለስ

Community

Andrew Giles MP Source: AAP

የአውስትራሊያ ፌዴራል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የአውስትራሊያ ሌበር ፓርቲ የመድብለባህላዊ ጉዳዮች ተጠሪ፤ አዲሱን የኢትዮጵያ ዘመን መለወጫ አስመልክተው መልካም ምኞታቸው በፓርቲያቸው ስም ይገልጣሉ።


በፌዴራል ሌበር ስም ለሁላችሁም መልካም አዲስ ዓመትን ልመኝ እወዳለሁ።

ወረርሽኙ ለእያንዳንዱ የአውስትራሊያ ማኅበረሰብ በእጅጉ ፈታኝ ነው።

 

በተለይም ከበርካታ ቤተሰቦቻቸውና ጓደኞቻቸው ተለይተው ላሉቱ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ። ምንም ጥርጣሬ የለውም፤ አገር ቤት ካለው ብርቱ አዋኪ ሁነት ጋር።

ይሁንና ይህ አዲስ ዓመት ለሁላችንም ሐሴትን እንደሚያጎናፅፈን ጥርጣሬ የለኝም።

ሁኔታው ሲፈቅድም አብሬያችሁ ለማክበር እሻለሁ።


Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now