አንኳሮች
- በዓለ ጥምቀት
- ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓቶች
- የበዓለ ጥምቀት ተምሳሌነት
- ሃይማኖታዊ ፋይዳዎች
- በረከተ ተሳትፎ
የጥምቀት በዓል ታላቅ በዓል ነው፤ ታሪካዊ በዓል ነው።የሜልበርን መካነ ሰላም ልደታ ለማርያም ወገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ፅዮን ቀሲስ እንግዳ ቸሩ
የጥምቀት በዓል የፍቅር በዓል ነው። በዓሉ በየዓመቱ በምዕመናኑ ተሳትፎ እያደገ እየሔደ ነው። ሰውና እግዚአብሔር አንድነታቸው የተጠበቀበት በዓል ነው። የጥምቀት ምስጢር ወደ ቤተ ክርስቲያን የመግቢያ በር ነው።በሜልበርን ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ቀሲስ ስንታየሁ አባተ
ጥምቀት ሃይማኖት ብቻ አይደለም፤ አይለይም። እንደ ጨዋ ሆኜ ሳየው፤ እንደ ሀገር አምባሳደርነት ነው። ምንም እንኳ ከሀገራችን ብንለይም፤ ሃይማኖታችንንና ባሕላችንን ሳንለቅ ለልጆች መተላለፉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንንና የኢትዮጵያን ቀጣይ መሆን ነው የሚያሳየው።"አቶ እሸቱ ሙሉጌታ፤ የሜልበርን ደብረ ሰላም መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያንና የሰበካ ጉባኤ አባል
የጥምቀት በዓልን በአማረ ሁኔታ እንዲደምቅ ላደረጉ የበዓሉ ዝግጅት ኮሚቴ አባላት፣ የሰበካ ጉባኤ አባላትንና የሜልበርንን ሕዝብ ሁሉ ላመሰግን እወዳለሁ።አቶ ኢሳያስ መለስ፤ የሜልበርን መካነ ሰላም ቅድስተ ልደታ ለማሪያም ወገብርኤል የሰበካ ጉባኤ አባል
የጥምቀት በዓል በፐርዝ ከተማ በጣም አስደናቂ ነው። ሶስት ዐቢያተ ክርስቲያናት ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱስ አማኑኤልና ደብረ መድኃኒት መድኃኒዓለም የአባቶችን ሥርዓት ተከትለው አንድ ላይ አክብረዋል።መልአከ ምህረት መምህር ዜናዊ፤ የደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል - ኪዳነ ምህረት አስተዳዳሪ፣ የምዕራብ አውስትራሊያ የትምህርትና ስብከት የትምህርት ኃላፊ





