ለወቅታዊና ስር የሰደዱ ችግሮች በየፈርጁ ልገሳዎችን ማድረግ ሰብዓዊነትን ማጉላቱ እውነት ነው። እንደማንኛውም አገርና ዜጋ ለኢትዮጵያም ከኢትዮጵያውያን ይበልጥ የሚቀርብም የሞራል ግዴታ ያለበትም የለም። ለኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን ‘ከባሕር ማዶ - አገር ቤት ችሮታዎችን ለማድረስና ራሳቸውንም ለመታደግ የግብረ ሰናይ ድርጅት ያሻቸዋልን?’ የሚለው መጠይቅም የማኅበረሰቡን አባላት ምላሽ ይሻል። ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ (ከብሪስበን)፣ አቶ ግርማ ፈይሳ (ከሲድኒ) እና አቶ አዳሙ ተፈራ (ከሜልበርን) ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።
Share






