‘ነብር ዝንጉርጉርነቱን ኢትዮጵያዊ ማንነቱን አይለውጥም’ እንዲሉ፤ ኢትዮጵያውያን የባሕር ማዶ ዜጋ ሆነው ቢኖሩም ኢትዮጵያዊ የማንነት ቁርኝታቸው ግና ከርሮ የተሳሰረ እንጂ ተበጥሶ የተጣለ አይደለም። ለሁለተኛ አገራቸውም ፍቅርና ታማኝነታቸው ሙሉዕ ነው። ወ/ሮ ዘለቃ መለሰ (ከአደላይድ)፣ ዶ/ር ሸሪፍ ሰዒድ (ከካንብራ) እና ዶ/ር ግርማ ሞላ (ከፐርዝ)፤ በኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን አንደበት አንድ አገር አቀፍ የግብረ ሰናይ ድርጅት ማቆም እንደሚያሻና እንደምንና በእነማን መዋቀር እንደሚገባው ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።
Share






