"ምርጫው እንከን የሌለው ባይሆንም የተሻለ ሰላማዊነት የታየበትና የፓርቲዎች ውድድርም የተስተዋለበት ነው" - አቶ አበራ ኃይለማሪያም

Abera Hailemariam, Acting President of CECOE.

Abera Hailemariam, Acting President of CECOE. Source: SBS Amharic/Demeke Kebede

አቶ አበራ ኃይለማሪያም - የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) ተጠባባቂ ዳይሬክተር፤ የኅብረቱን ዋነኛ የታዛቢ ምልከታ ግኝቶች አስመልክተው ለSBS አማርኛ የአገር ቤት ዘጋቢ ደመቀ ከበደ አብራርተዋል።


በስድስተኛው አገራዊና ክልላዊ ምርጫ የሲቪል ማህበራትን ተሳታፊነት ለማረጋገጥ እንዲያስችል 176 ማህበራት በጋራ በመሆን የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ሕብረት ለምርጫ የተሰኘ ድርጅትን መስርተው ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል።

ኅብረቱ ገለልተኛ እና ከፓርቲ ፖለቲካ ነፃ የሆነ ድርጅት ሲሆን ምርጫው አካታችና ግልፅነት የተሞላበት መሆኑን ለማረጋገጥ የሚሰራ ድርጅት ነው። ዛሬ በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል በሰኔ 14፣ 2013 በተካሄደው ምርጫ ላይ  ህብረቱ በሰበሰበው መረጃ ላይ የተመሰረተ ቅድመ ግኝትን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫው በምርጫ ቀን ለረጅም ሰዓታት በሰልፍ ላይ በመቆየት ድምፃቸውን የሰጡ ዜጎችን፣ የምርጫ ቦርድን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና እጩዎቻቸውን፣ የፀጥታ ሀይሎችን እንዲሁም በምርጫው ሂደት ላይ የተሳተፉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን አድንቋል።

ኅብረቱ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤቶች ምርጫ ባካሄደባቸው ሰባት ክልሎች እና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች፤ ከ3000 በላይ የሚሆኑ ቋሚ እና ተንቀሳቃሽ ታዛቢዎችን እንዳሰለጠነ የገለፀው ህብረቱ  ቋሚ ታዛቢዎች የታዘቧቸውን መረጃዎች በአዲስ አበባ ወደሚገኘው የሕብረቱ የመረጃ ማዕከል በጽሁፍ መልዕክት የላኩ ሲሆን፤ ተንቀሳቃሽ ታዛቢዎች ደግሞ በሚኖሩበት አካባቢ ያሉ ከምርጫ ጋር የተገናኙ ሂደቶችን እንዲሁም የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን ከአንድ ምርጫ ጣቢያ ወደሌላ በመዘዋወር መታዘባቸውን አብራርቷል።

ታዛቢዎቹ የምርጫ ጣቢያዎችን ዝግጅት፣ አከፋፈት፣ የድምፅ አሰጣጥ እና ቆጠራ እንዲሁም የድምፅ ቆጠራ ውጤት በሚለጠፍበት ጊዜ የነበሩ ሁኔታዎችን እንደታዘቡ አመልክቷል። ከቋሚ ታዛቢዎች በተጨማሪ ከ150 በላይ ተንቀሳቃሽ ታዛቢዎችን በማሰማራት በተንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች የተከሰቱ አሳሳቢ ኩነቶችን ለመረጃ ማዕከሉ እንዲልኩ እንዳስደረገና ከዚህም በመነሳት የህብረቱ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ከምርጫ አሠራር ጋር ተያያዥነት ያላቸውን የምርጫ ምልከታ ግኝቶች ዋና ዋና ነጥቦች ዛሬ ይፋ አድርጓል።


Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service