ከኢትዮጵያውያን ማንንት መገለጫ አንዱ ልዩ የሆነ የቀን መቁጠሪያችን ነው ። ምንጩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ቢሆንም አገልግሎቱ ግን ለመላው ኢትዮጵያውያን ነው በዚህም ልንኮራ ይገባናል፤ የሚሉን መጋቢ ምስጢር ቀሲስ ስንታየሁ በምስራቅ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት የሜልበርን ምእራፈ ቅዱሳን ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያ አስተዳዳሪ እንዲሁም መጋቢ ጥበብ ቀሲስ ቴዎድሮስ በሜልበርን ደብረገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አገልጋይ ናቸው።
አንኳሮች
- የጳጉሜ ወር ቀናት ስሌት
- የቀን መቁጠሪያን ከሌሎች ለምን ተለየ
- የቀን መቁጠሪያን ቀመር ለትውልዱ እንዴት እናስተምር
Share





