ሼክ አብዱራህማን ሀጂ ከቢር በአውስትራሊያ የእስልምና እምነት ተከታዮች መሪ የኢትዮጵያን አዲስ አመት በአልን በማስመልከት ሲናገሩ ፤ ኢትዮጵያን እጎዳለሁ የሚል መጨረሻ የለውም ፤ መጨረሻ ያለው እግዚአብሄርን የሚፈራ ብቻ ነው ፡፡ አገርን መውደድ የሀይማኖታችን አካል ነው፡፡ አገር ክርስቲያን እና እስላም አይልም ለሁሉም አገር አንድ ነች ፡፡ ከአገር ወጥተናል በማለት ከሃላፊነታችን ወደኋላ ማለት አንችልም ብለዋል ፡፡
Share






