በተለይ በኮቪድ19 ወቅት እየጨመረ የመጣውን የቤተሰብ አመጽን እና በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመቀነስ ምን መደረግ አለበት በሚሉት ዙሪያ ለአባለቱ መረጃዎችን እና የተለየዩ ድጋፎችን ሲያቀርቡ እንደቆየ ዶ/ር እማዬነሽ ስዮም በቪክቶርይ የሴቶች ህብረት ፕሬዝደንት፤ ጽጌረዳ መኮንን የህብረቱ ምክትል ፕሬዝደንት እና ሃና ታደሰ የህብረቱ ጸሃፊ ገልጸውልናል ፡፡አያይዘውም በቪክቶርያ በመንግስት የተቀመጠው የደረጃ 4 ክልከላ በየግላቸው ያሳያቸውንና ያስተማራቸውን የህይወት ልምድ ገልጸውልናል ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም “ በቅርቡ ጤናማ የቤተሰብ ግንኙነት ለጤናማና ለጠንካራ ማህበረሰብ ” በሚል ርእስ ስለሚያዘጋጁት የመረጃ ልውውጥ መርሃ ግብር ነግረውናል ፡፡
Share






