Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

" አባቴ እግዚአብሄር ይባርክህ " - በቅርቡ በሞት የተለየው የአቶ ሰሎሞን አዲስ ታምሩ የመጨረሻ የስንብት ቃል እና ሽኝት

Solomon Addis .jpg

አቶ ሰሎሞን አዲስ ታምሩ ባደረበት ህመም ሳቢያ ሚያዚያ 22 ቀን 2026 ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል ። አቶ ሰለሞን ወደ አውስትራሊያ ለመጀመሪያ የመጡት የአቶ አዲስ ታምሩ ሁለተኛ ልጅ ሲሆን ፤ እናቱ ወ/ሮ ሊሊያን ኒኮላስ የአቦርጅናል ዝርያ ያላቸው ናቸው። የጸሎት እና ሽኝት ስነ ስርአቱም በደብረ ሰላም መድሃኒአለም ሜልበርን ቤተክርስቲያን ተከናውኗል። ስርአተ ቀብሩም ሰኞ ሜይ 21 ቀን 2026 በሜልበርን ተፈጽሟል። በሽኝት ስነስርአቱ ላይ በሜልበርን እና በአውስትራሊያ የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ወዳጅ ዘመዶች ተገኝተዋል ። በስፍራው ከተገኙት መካከልም ፤ መላክ ጸሃይ ቀሲስ መንግስቱ ሀይሌ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያ የምስራቅ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ አህጉረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ እንዲሁም የብሪዝበን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ : መላከ አርአያም ቀሲስ ተስፋ ኅሩይ - የሜልበርን ደብረሰላም መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ : አቶ እሸቱ ሙሉጌታ ፤ ወ/ሮ ተኛኜ ወርቅ ብስራት ፤ ጄሰን አዲስ ታምሩ ( ወንድም ) ፤ ታሻ ፊትዝክላረንስ (ሚስት) ወ/ሮ ቅድስት ደስታ ፤ አቶ አበራ አያሌው እና ወ/ሮ ቆንጂት ጥላሁን የተሰማቸው ህዘን ገልጸዋል።


አንኳሮች
  • በአውስትራሊያ የመጀመሪያው ሰፋሪ ልጅ እረፍት
  • የልጅነት ጊዜ እና አስትዳደግ
  • የሀይማኖት አባቶች የሽኝት መልእክት
  • የማህበረሰቡ አባላት መልእክቶች

Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now