በየዓመቱ ወርኃ ሴፕቴምበር በገባ የመጀመሪያው ሳምንት እሑድ የአባቶች ቀን በምድረ አውስትራሊያ ተከብሮ ይውላል። በልጆች ሕይወት ውስጥ አባቶችና አባታዊ አርአያ ሆነው ላሉም ሆነ ላለፉ ለቸሩት ፍቅር፣ ማለፊያ ጥረቶቻቸውንና ድካማቸውን ሞገስ ለማላበስ። አቶ ዳንኤል ዘውዱ፣ አርቲስት ጌታሁን ሰሎሞንና አቶ መብራቱ ጎበና ስለ አባቶች ቀን ፋይዳና ትዝታዎቻቸው ያወጋሉ። ታዳጊ ልጆችም ለአባቶቻቸው የ ‘እንኳን አደረሰህ’ መልዕክቶችን ያስተላልፋሉ።
Share






